ዓለምአቀፋዊ ዜና

የትዊተር ኩባንያ በ44 ቢሊዮን ዶላር ተሸጠ

By ዮሐንስ ደርበው

April 26, 2022

ከሁለት ዓመታት በፊት ራሳቸው ኢሎን መስክ በትዊተር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት አንድ መልዕክት በትዊተር ኩባንያ እንዲወርድ ሲደረግባቸው፥ ሀሳቤን የመግለጽ መብቴን ልታፍኑ አትችሉም ሲሉ ከፍተኛ ቅሬታ አሰምተው እንደነበር ይተወሳል።

አሁን ተዊተርን ጠቅልለው በእጃቸው ያስገቡት የዓለማችን ቁጥር አንድ በለፀጋ፥ ትዊተርን “የሀሳብ ነፃነት መንሸራሸሪያ መድርክ አረድገዋለሁ “ ሲሉ ቃል ገብተዋል።

የሌሎች በርካታ ድርጅቶችና ኩባንያዎች ፈጣሪ፥ ባለቤትና ባለድርሻ የሆኑት ኢሎን መስክ፥ የተዋቂዎቹ በኤሌክትሪክ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች አምራች የሆነው የቴስላ ኩባንያ እና በአሜሪካ የጠፈር ምርምር ቴክኖሎጅ ኮርፖሬሽን የሆነው ሰፔስ ኤከስ ኩባንያ መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚም ናቸው።

ደቡብ አፍሪካ ተወላጅ የሆኑት የ51 ዓመቱ ኢሎን መስክ፥ በያዝነው ወር ላይ 273 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ሀብት በማስመዝገብ በቢሊየነሮቹ ደረጃ አውጪ ፎርብስ መጽሄት የዓለማችን ቁጥር አንድ ባለሀብት መባል ችለዋል፡፡

በተለይም በህዋ አካላት ኢንዱስትሪ ላይ ስር ነቀል የሆነ አብዮት በማካሄድ የሰው ልጅ የህዋ (የስፔስ) ላይ በረራን በቀላል ወጪ ሊጠቀምበት የሚችልበትን ተስፋ ዕውን ለማድረግ በማለም ከ20 ዓመታት በፊት ስፔስ ኤክስን ( SpaceX) የፈጠሩ ምጡቅ የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ጎልማሳ ባለሃብት ናቸው ኢሎን መስክ።

ከካናዳዊት እናትና ከደቡብ አፍሪካዊ አባት የተወለዱት እኝህ ባለፀጋ፥ ደቡብ አፍሪካዊ፥ አሜሪካዊና ካናዳዊ ዜግነት አላቸው።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!