የሀገር ውስጥ ዜና

ኤች አር 6600 እና ኤስ 3199 ረቂቅ ህጎች እንዳይጸድቁ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በጋራ መቆም እንዳለባቸው ምሁራን ጠየቁ

By Feven Bishaw

April 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኤች አር 6600 እና ኤስ 3199 ረቂቅ ህጎች እንዳይጸድቁ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በጋራ መቆም አለባቸው ሲሉ የፖለቲካ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁራን ተናገሩ፡፡

በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሴኔሳ ደምሴ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ÷የፖለቲካ ልዩነቶች ቢኖሩም እንኳ የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በአንድነት መቆም አለባቸው ብለዋል።