አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ከተጣለበት አገራዊ ሀላፊነት አንጻር የሁሉንም ዜጎች ተሳትፎ ያረጋገጠ እና ከወገንተኝነት የጸዳ መሆን ይገባዋል ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ፥ በቀጣይ በኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አማካኝነት በሚደረጉ አገራዊ ውይይቶች ላይ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ መዘጋጀታቸው ተናግረዋል።