አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ማሽኖች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ መፈቀዱን ተከትሎ ባለፉት ሁለት አመታት የሜካናይዜሽን ግብርናውን ሊያዘምኑ የሚችሉ ማሽኖች ቁጥር ማደጉን ግብርና ሚኒስቴር ገልጿል።
ለግብርናው ዘርፍ አገልግሎት ያላቸው ማሽኖች ከረጥ ነፃ እንዲገቡ የሚያስችል የፖሊሲ ለውጥ ተደርጎ አርሶ አደሩ የግብርና ማሽኖችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ እድል ተሰጥቷል፡፡