የሀገር ውስጥ ዜና

የግብርና ማሽኖች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ በመፈቀዱ የሜካናይዜሽን ግብርናን ሊያዘምኑ የሚችሉ ማሽኖች ቁጥር አድጓል – የግብርና ሚኒስቴር

By Feven Bishaw

April 27, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ማሽኖች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ መፈቀዱን ተከትሎ ባለፉት ሁለት አመታት የሜካናይዜሽን ግብርናውን ሊያዘምኑ የሚችሉ ማሽኖች ቁጥር ማደጉን ግብርና ሚኒስቴር ገልጿል።

ለግብርናው ዘርፍ አገልግሎት ያላቸው ማሽኖች ከረጥ ነፃ እንዲገቡ የሚያስችል የፖሊሲ ለውጥ ተደርጎ አርሶ አደሩ የግብርና ማሽኖችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ እድል ተሰጥቷል፡፡