ዓለምአቀፋዊ ዜና

የተባበሩት መንግስታት ለአፍሪካ ቀንድ የድርቅ መቋቋሚያ የሚውል 1 ቢሊየን ዶላር ለመስጠት ቃል ገባ

By Feven Bishaw

April 27, 2022

አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 19፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በጀኔቫ ባካሄደው ጉባኤ ለአፍሪካ ቀንድ ድርቅ መቋቋሚያ የሚውል 1 ቢሊየን ዶላር ለመስጠት ቃል ገብቷል፡፡

በተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ከለጋሽ አካላት የተሰበሰበው ይህ ገንዘብ በድርቅ ለተጎዱት ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማቅሰብ የሚውል ነው ተብሏል፡፡