Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ከዩኒሴፍ ዋና ዳይሬክተር ካትሪን ራስል ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 19 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ አዲስ ከተሾሙት የዩኒሴፍ ዋና ዳይሬክተር ካትሪን ራስል ጋር ተወያይተዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ በኢትዮጵያ በሰው ሠራሽና በተፈሮ አደጋ የተጎዱ በርካታ ሕጻናትን ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ለማየትና ለመርዳት የሚያስችላቸውን የዓለም አቀፍ ከፍተኛ ድጋፍ ለማስገኘት ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውን የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዩኒሴፍ በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የመስክ ሥራ ልምድ ያለው ሲሆን ግንኙነቱን በማሻሻልና በማጠናከር መስራት እንዳለበት ጠቁመዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.