አዲስ አበባ፣ሚያዝያ20፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቪላድሚር ፑቲን በዩክሬን ግጭት ጣልቃ በሚገባ ሀገር ላይ ሀገራቸው መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም አፀፋውን እንደምትመልስ አስጠነቀቁ።
ፕሬዚዳንቱ ከሀገሪቱ የህግ አውጪ ምክር ቤት አባላት ጋር በሞስኮ ተገናኝተው በተወያዩበት ወቅት እንደተናገሩት፥ የውጭ ሀይሎች በዩክሬን ጦርነት ውስጥ ጣልቃ የሚገቡ ከሆነ ሀገራቸው “ማንም ሀገር ያልታጠቃቸው” ያሏቸውን ዘመናዊ መሳሪያዎች በመጠቀም መብረቃዊ ምላሽ ትሰጣለች ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡