የሀገር ውስጥ ዜና

የሀገራችንን መጥፋት የሚፈልጉ ሁሉ የጥፋት ዕቅዳቸው ወኪል አድርገው እንዲወስዱን ልንፈቅድ አይገባም-ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

By Feven Bishaw

April 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገራችንን መጥፋት የሚፈልጉ ሁሉ የጥፋት ዕቅዳቸው ወኪል አድርገው እንዲወስዱን ልንፈቅድ አይገባም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፥ እንደ ህዝብ ልዩነቶቻችንን አምነን ተቀብለን በብዙ ትውልዶች ዕድሜ በኁባሬ ተሣሥረን ኖረናል ብለዋል።