የሀገር ውስጥ ዜና

በነገው ዕለት በመዲናዋ ከሚካሄደው የኢፍጣር መርሃ ግብር ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉ

By Feven Bishaw

April 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር መርሃ ግብር ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የፀጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

የከተማዋን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከመላው ሠላም ወዳድ ህዝብ ጋር ሆኖ ተግባሩን በመወጣት ላይ የሚገኘው የፀጥታና የደህንነት ግብረ ኃይል የታላቁን ረመዳን ፆምን አስመልክቶ ለሚደረገው የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሃ ግብር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል፡፡