የሀገር ውስጥ ዜና

የዲፕሎማሲ ሥራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ በመሥራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መንቀሳቀስ እንደሚገባ ተገለፀ

By Feven Bishaw

April 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወቅታዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረጉ የዲፕሎማሲ ሥራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ በመሥራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መንቀሳቀስ እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የ2014ዓ/ም በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ዛሬ ከዋናው መስሪያ ቤት እና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል።