የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ ዕርዳታ ያለምንም ገደብ ወደ ትግራይ ክልል እንዲደርስ እያደረገ ነው – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

By ዮሐንስ ደርበው

April 29, 2022

የውጭ አገራት ለጋሾች እጅ ማጠር እና በሃገር ውስጥ የተረጅዎች ቁጥር መጨመር በሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ላይ ችግር እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ህወሐት ከአርቢቲ፣ በረሃሌ እና ከአብአላ ውጭ ከሌሎች በወረራ ከያዛቸው የአፋር አካባቢዎች እንዳልወጣ እና አሁንም ድረስ አንዳንድ የአማራ ክልል ቀበሌዎችን ይዞ እንደሚገኝ ነው በመግለጫቸው ያመላከቱት።

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሰብአዊ እርዳታዎችን እንዲያደርግና ህወሓት በኃይል ከያዛቸው አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ ግፊት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ህወሓት በዚህ ሰዓትም ጥቃት ሊፈፅም እንደሚችልም ዛቻ መሰል መልዕክት እያስተላለፈ እንደሚገኝ አምባሳደር ዲና አመልክተዋል።

እስካሁን ከ15 ሺህ 300 በላይ ዜጎች ከሳዑዲ እንደተመለሱ ጠቅሰው÷“ ከኢድ እስ ኢድ„ ወደ ሃገር ቤት መርሃ ግብር ዳያስፖራው ዘመድ እንዲጠይቅ፣ የኢትዮጵያን ባህላዊ እና ታሪካዊ መስህቦች እንዲያስተዋውቅ እና ለሀገር ልማትና ሰላም የበኩላቸውን እንዲወጡ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

ከኢድ እስከ ኢድ በሚል የተጀመረው መርሃ ግብር በአሁኑ በዓል ብቻ የሚቆም ሳይሆን በቀጣይም በተለያዩ ሃይማኖታዊ እና ህዝባዊ በዓላት ላይ ዜጎች ለአገራቸው የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ በቀጣይነት እንዲከናወን የሚደረግ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አክለውም÷ የኬንያው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሙዋይ ኪባኪ ህልፈትን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በስርዓተ ቀብራቸው ለመገኘት ወደ ቦታው ማቅናታቸውን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከአፍሪካ መድሃኒት አቅራቢ አጀንሲ ጋር መድሀኒቶች በተሻለ ጥራት እንዲሸጡ እና ተአማኒ እንዲሆኑ በሚያስችል ጉዳይ ላይ 29ኛ አገር ሆና መፈራረሟን ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ እና በሱዳን ያለውን የድንበር ጉዳይ ችግር ለመፍታት÷ በሁለቱ አገሮች የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት የጋራ ኮሚሽኖች እየሰሩ ነው ብለዋል።