የሀገር ውስጥ ዜና

በጎንደር የተፈጠረውን ክስተት ተከትሎ ግጭትን ለማስፋፈት እየሰሩ ያሉ የግጭት ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ መንግስት አሳሳበ

By Melaku Gedif

April 29, 2022

ጎንደር ከተፈጠረው ክስተት ጋር በተያያዘ እስካሁን በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ሚኒስትሩ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።

ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተጨማሪ ግጭት እና ጥፋት እንዲፈጠር እየሰሩ ያሉ አካላት አሉ ያሉት ሚኒስትሩ፥ በዚህ አፍራሽ ተግባር እየተሳተፉ ያሉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።

ችግሩን ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት እየሰሩ ያሉ አካላትን መንግሥት እንደማይታገስ በመጥቀስም፥ ወንጀልን በወንጀል ለማካካስ የሚደረግ ማንኛውም ጥረት ከወንጀል ፈፃሚነት ተለይቶ አይታይም ብለዋል።

የአማራን ህዝብ በሃይማኖት፣ በብሔር እና በአካባቢ ለመከፋፈል የሚሰሩ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ መንግሥት አሳስቧል።

መላው ህዝብ የጽንፈኞችን ሴራ በመገንዘብ ሴራቸውን ለማክሸፍ ከመንግሥት ጋር በትብብር እንዲሰራም ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል መንግሥት በአሸባሪው ሸኔ ላይ የተከፈተው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉን እና በዚህም በቡድኑ ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ መድረሱን ገልጸዋል።

ወደ ትግራይ ክልል የዕለት ደራሽ እርዳታ፣ መድሃኒት እና የሕክምና ቁሳቁስ የማጓጓዙ ጥረት በየብስ እና በአየር ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰዋል።