የሀገር ውስጥ ዜና

ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ በጎንደር የተፈጠረው ክስተት የክርስትናንም ሆነ የእስልምና እምነቶችን አይወክልም- የጎንደር ከተማ አስተዳደር

By Feven Bishaw

April 30, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ የተፈጠረው ክስተት የክርስትናንም ሆነ የእስልምናን እምነቶች እንደማይወክል የጎንደር ከተማ አስተዳደር ገለጸ፡፡

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዘውዱ ማለደ ወቅታዊ የጎንደር ከተማ ጉዳይን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡