የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ለእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ማዕድ አጋሩ

By Feven Bishaw

April 30, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በተገኙበት ለእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ማዕድ አጋርተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ የማዕድ ማጋራት ድጋፉን ያደረጉት በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የአካባቢው የእስልምና እምነት ተከታዎች ነው።