ህዝበ ሙስሊሙ ኢድ አልፈጥር በዓልን ሲያከብር አብሮነትን፣ መደጋገፍንና መቻቻልን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባል- አቶ ኦርዲን በድሪ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)ህዝበ ሙስሊሙ ኢድ አልፈጥር በዓልን ሲያከብር አብሮነትን፣ መደጋገፍንና መቻቻልን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባል ሲሉ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለጹ፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ 1443ኛውን የኢድ አልፈጥር በዓል አስመልክቶ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡