የሀገር ውስጥ ዜና

በቀድሞ የመከላከያ መኮንኖች የክስ መዝገብ ላይ 1ኛ ተከሳሽ ሕይወት ማለፍን ተከትሎ በሌሎች ተከሳሾች ላይ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ

By Feven Bishaw

May 03, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀድሞ የመከላከያ መኮንኖች የክስ መዝገብ ላይ 1ኛ ተከሳሽ ሜጀር ጀኔራል ገብረመድህን ፍቃዴ(ወዲ ነጮ) ድንገተኛ ሕይወት ማለፍን ተከትሎ በሌሎች ተከሳሾች ላይ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱ ተገለፀ ።

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረ ሽብርና የህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ለዛሬ ተይዞ በነበረው ተለዋጭ ቀጠሮ ቀሪ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ተሰይሞ ቀሪ 7ኛ እና 15ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ቃላቸውን ለመስጠት ተገኝተው ቃለ መሀላ ፈፅመው ነበር ።