ከሳዑዲ 1 ሺህ 29 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳኡዲ አረቢያ የመመለስ ስራ በአጠቃላይ ቁጥራቸው 1 ሺህ 29 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ ዜጎች ውስጥ አምስት ህጻናትና 1 ሺህ 24 ወንዶች መሆናቸውን ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢውን ድጋፍ እና ክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማእከላት እንዲሄዱ መደረጉም ነው የተገለጸው፡፡
እስካሁን በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ስራ ቁጥራቸው ከ18 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን፡፡