የሀገር ውስጥ ዜና

ግምታቸው ከ9 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የኮንትሮባንድ ሲጋራዎችና ልባሽ ጨርቆች ተያዙ

By Feven Bishaw

May 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ሸዋ ዞን መተሓራ ከተማ ግምታቸው ከ9 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የኮንትሮባንድ ሲጋራዎችና ልባሽ ጨርቆች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ።

የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ዲቭዥን ሃላፊ ኮማንደር አስቻለው ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት የኮንትሮባንድ ሲጋራዎችና ልባሽ ጨርቆቹ ከአዋሽ ሰባት ወደ አዳማ በመጓጓዝ ላይ እንዳሉ ትናንት እኩለ ለሊት ላይ በፀጥታ ሃይሎች ክትትል ተይዘዋል።