አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2014 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ወጣቶች ህብረት በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች የምርጥ ዘር ድጋፍ አደረገ፡፡
በክልሉ ድርቅ በተከሰተባቸዉ 7 ዞኖች የበልግ ዝናብ መጣል መጀመሩን ተከትሎ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ወደ ግብርና ስራቸዉ እንዲመለሱ ለማድረግ ድጋፉ እንደተደረገ የኦሮሚያ ወጣቶች ማህበር ፅ/ቤት ሀላፊ ወጣት ገዛኸኝ አንዳርጌ ተናግሯል፡፡