የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ወጣቶች ህብረት በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የምርጥ ዘር ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

May 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2014 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ወጣቶች ህብረት በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች የምርጥ ዘር ድጋፍ አደረገ፡፡

በክልሉ ድርቅ በተከሰተባቸዉ 7 ዞኖች የበልግ ዝናብ መጣል መጀመሩን ተከትሎ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ወደ ግብርና ስራቸዉ እንዲመለሱ ለማድረግ ድጋፉ እንደተደረገ የኦሮሚያ ወጣቶች ማህበር ፅ/ቤት ሀላፊ ወጣት ገዛኸኝ አንዳርጌ ተናግሯል፡፡