የሀገር ውስጥ ዜና

ለሥራ ፈላጊው ወጣት ሥራ ለመፍጠር ሚኒስቴሩ ከተለያዩ አደረጃጀቶች ጋር መክሮ የመፍትሄ አቅጣጫ ያስቀምጣል – አቶ ንጉሡ ጥላሁን

By Feven Bishaw

May 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሥራ ፈላጊው ወጣት ሥራ ለመፍጠር የሚሰሩ ጣቢያዎች ያሉባቸውን ችግሮች ለመቅረፍ ሚኒስቴሩ ከተለያዩ አደረጃጀቶች ጋር መክሮ የመፍትሄ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ገለጹ።

የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ከክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ አስተባባሪዎች እና የቢሮ ኃላፊዎች ጋር በአዳማ ከተማ ያካሄደውን መድረክ ዛሬ አጠናቋል።