አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2014 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለ2014/15 የመኽር ምርት ዘመን ጅቡቲ ወደብ ከደረሰው 7 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 75 በመቶው ወደ ማዕከላዊ መጋዘን መግባቱን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን ተናገሩ።
ሚኒስትሩ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷ ወደ ሀገር ውስጥ ከገባው የአፈር ማዳበሪያ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል ነው ያሉት።