የሀገር ውስጥ ዜና

የአፋር ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ

By Feven Bishaw

May 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2014 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን የአፋር ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

በዘንድሮው በጀት ዓመት ገቢ በዘጠኝ ወራት 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን የቢሮው ኃላፊ አቶ መሀመድ ሀሰን ገልጸዋል።