የሀገር ውስጥ ዜና

የባህልና ስፖርት ሚኒስትሩ ከቻይና መንግስት ኮንስትራክሽን እና ኢንጂነሪንግ ካምፓኒ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

May 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2014 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የባህልና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ ከቻይና መንግስት ኮንስትራክሽን እና ኢንጂነሪንግ ካምፓኒ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ ዙሪያ ተወያዩ።

በውይይቱ አቶ ቀጄላ በካምፓኒዉ የቀረበ የዋጋ ማስተካከያ ጥያቄን በተመለከተ የዶላር ቅድመ ክፍያ ሳይከፈል በመቆየቱ፣ የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ ከዜ ወደ ጊዜ እየናረ መሄዱን ተከትለዉ የብሔራዊ ስቴድየሙ ግንባታ ሂደት ላይ መጓተት በመፍጠሩ አጠቃላይ የአለም የዋጋ ማስተካከያ መርሆን መሰረት ያደረገ ዋጋ ማስተካከያ እንደሚደረግ ለተቋራጭ ካምፓኒዉ አረጋግጠዋል።