የሀገር ውስጥ ዜና

ባለስልጣኑ ከቅርሶች እድሳት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት የተጠናከረ ስራ መጀመሩን ገለጸ

By Tibebu Kebede

March 03, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣2012 (ኤ ቢ ሲ) በሀገሪቱ ከሚገኙ ቅርሶች እድሳት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት የተጠናከረ ስራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን አሰታውቋል።

ለእደሳቱ ስራ የሚደረገው ጥናት መጀመሩን የገለጹት አቶ ሃይሉ ፥ ይህም እስከ ታህሳስ 2013 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድ አንስተዋል።

የጥናት ውጤቱን ተከትሎም ተግባራዊ የጥገና ስራው ይጀመራል ብለዋል።

በሹመት አለማየሁ