የሀገር ውስጥ ዜና

2 ነጥብ 43 ቢሊየን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል – የኢንቨስትመንት ኮሚሽን

By ዮሐንስ ደርበው

May 10, 2022

203 ባለሀብቶች ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ ታቅዶ 118 ባለሀብቶች መሰማራታቸውን ገልጸው፥ ከዚህም ውስጥ 65ቱ በማኑፋክቸሪንግ 50 ያህሉ ደግሞ በአገልግሎትና ሦስቱ በግብርና ዘርፍ መሰማራታቸውን አብራርተዋል፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ከሚላኩ ምርቶች 223 ሚሊየን ዶላር ለማግኘት መታቀዱን እና 156 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር ተገኝቷል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ27 ሚሊየን ዶላር ጭማሪ ማሳየቱን ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ በመግለጫቸው አመላክተዋል፡፡