በፕሪሚየር ሊጉ ድሬዳዋ ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን በሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ23ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን በሰፊ የጎል ልዩነት አሸንፏል፡፡
ረፋድ 4 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በማሸነፍ ወሳኝ 3 ነጥብ ከባህርዳር ስታዲየም ማግኘት ችሏል፡፡
ለድሬዳዋ ከተማ ሄኖክ አየለ እና አብዱራህማን ሙባረክ ሁለት ሁለት ጎሎችን በስማቸው ማሰቆጠርችለዋል፡፡
ድሬዳዋ ዛሬ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 27 በማድረስ ከወራጅ ቀጠና ስጋት መውጣት ሲችል÷ሃዲያ ሆሳዕና ወደ 6ኛ ደረጃ የሚመጣበትን እድል አምክኗል፡፡