የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ክልል በበልግ እርሻ 400 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል

By Feven Bishaw

May 12, 2022

አዲስ አበባ ፣ግንቦት 4 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል እየተካሄደ ባለው የበልግ እርሻ እንቅስቃሴ እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ 400 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው እንደገለጹት፥ በዘር የተሸፈነው መሬት በክልሉ በ2014/2015 ምርት ዘመን በተለያየ ሰብል ለማልማት ከታቀደው 1 ሚሊየን ሄክታር ውስጥ ነው።