የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ መላኩ አለበል ከሶፍሌት ማልታ ኢትዮጵያ ሼር ካምፓኒ ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

May 12, 2022

አዲስ አበባ፣ግንቦት 4፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ከሶፍሌት ማልታ ኢትዮጵያ ሼር ካምፓኒ ስራ አስኪያጅ ጃን ቦንት ቪቬት ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸው ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል÷ ብቅል አማራች ካምፓኒው ሶፍሌት ማልታ በኢትዮጵያ እደረገ ያለውን ጥሩ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በመገንዘብ ሚኒስቴር መስሪ ቤቱ ለድርጅቱ የኢንቨስትመንት እገዛ እንደሚያደርግ ገልፀዋል፡፡