አዲስ አበባ፣ግንቦት 4፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ከሶፍሌት ማልታ ኢትዮጵያ ሼር ካምፓኒ ስራ አስኪያጅ ጃን ቦንት ቪቬት ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸው ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል÷ ብቅል አማራች ካምፓኒው ሶፍሌት ማልታ በኢትዮጵያ እደረገ ያለውን ጥሩ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በመገንዘብ ሚኒስቴር መስሪ ቤቱ ለድርጅቱ የኢንቨስትመንት እገዛ እንደሚያደርግ ገልፀዋል፡፡