የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በ60 ሚሊየን ዩሮ የተገነባውን የብቅል ፋብሪካ መረቁ

By Feven Bishaw

May 13, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተገነባው ሱፍሌ ማልት የብቅል ማምረቻ ፋብሪካ ተመረቀ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው÷ “ዛሬ በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ያስመረቅነውና የኢንቪቮ ግሩፕ ኢንቨስትመንት የሚመሰገን ነው” ብለዋል።