የሀገር ውስጥ ዜና

የአፋር ክልል በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የ 10 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

May 13, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል በሶማሌ ክልል በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖች የ10 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉን የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ጅግጅጋ ከተማ በመገኘት ለሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ አስረክበዋል።