ዓለምአቀፋዊ ዜና

ፊንላንድ ኔቶን ለመቀላቀል ወሰነች

By Feven Bishaw

May 15, 2022

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፊንላንድ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) መቀላቀል እንደምትፈልግ በይፋ አስታወቀች።

የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳውሊ ኒኒስቶ ከካቢኔያቸው ጋር በነበራቸው ስብሰባ፥ ፊንላንድ የኔቶ አባል ለመሆን በምታቀርበው የአባልነት ጥያቄ ላይ ተስማምተዋል።