አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት የሰብዓዊ መብት ጥሰት የምርምራ ውጤት ምክረ ሀሳብን ተግባራዊ ለማድረግ ያለው ዝግጁነት አበረታች መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ።
ምክትል ኮሚሽነሯ ወይዘሮ ራኬብ መሰለ፥ ኮሚሽኑ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ሰብዓዊ መብቶችን ማሳወቅና ማስተማር፣ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችና ሕጎች ተፈጻሚነትን መከታተል እንዲሁም የልማት ፕሮግራሞች ሲታቀዱ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮችን ማካተታቸውን የማረጋገጥ ስራ ሰርቷል ብለዋል።