የሀገር ውስጥ ዜና

መንግሥት ለክልሉ አርሶ አደሮች ከምርት እስከ ገበያ ትስስር ያመቻቻል -አቶ ሙስጠፌ መሃመድ

By Feven Bishaw

May 15, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ በክልሉ ፋፈን ዞን ደጋህሌ ከተማ በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ ዜጎች ለገበያ ያቀረቡትን ፍራፍሬ ጎብኝተዋል።

የደጋህሌ ከተማ ለግብርና ምቹ ከሆኑ የክልሉ ከተሞች አንዷ ስትሆን አርሶ አደሮች የሚያመርቱትን ፍራፍሬ ለአካባቢው በተለይ ለጅግጅጋ ከተማ ገበያ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል፡፡