አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከፊል የጨረቃ ግርዶሽ ዛሬ ንጋት መታየቱን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ እስፓሻል ኢኒስቲቲዩት አስታውቋል፡፡
ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢኒስቲቲዩት እንዲሁም ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ጋር በመተባበር የጨረቃ ግርዶሽ ትዕይንት ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ለሠመራና አካባቢ ህብረተሰብ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ተከናውኗል።