የሀገር ውስጥ ዜና

ኢዜአ ያሰባሰበውን ከ5ሺህ በላይ መፅሐፍት ለአብርሆት ቤተ- መጻሕፍት አስረከበ

By Feven Bishaw

May 16, 2022

አዲስ አበባ፣ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከተቋሙ ሠራተኞችና ከሌሎች አካላት ያሰባሰበውን ከ5ሺህ በላይ መፅሐፍት ለአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት አስረከበ።

ለአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት “ሚሊዮን መፅሐፍት ለሚሊኒየሙ ትውልድ” በሚል መሪ ኃሳብ ለአንድ ወር የሚቆይ መፅሐፍትን የማሰባሰብ ጥሪ ተከትሎ በርካታ ተቋማትና ግለሰቦች ምላሽ እየሰጡ ነው።