የሀገር ውስጥ ዜና

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኢንቨስትመንት ማነቆዎችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አቶ አሻድሊ ሃሰን ገለጹ

By Feven Bishaw

May 16, 2022

 

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኢንቨስትመንት ማነቆዎችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን አስታወቁ።

የክልሉ የኢንቨስመንት ፎረም “ሃላፊነት የተላበሰ የግብርና ኢንቨስትመንት ለሁለንተናዊ ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ በአሶሳ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።