የሀገር ውስጥ ዜና

በሐረሪ ክልል መሬት አጥረው በተቀመጡ ባለሃብቶች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው

By Feven Bishaw

May 16, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል መሬት አጥረው በተቀመጡ ባለሃብቶች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በኢንቨስትመንት ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን፥ በክልሉ ለሚገኙ ባለሃብቶች ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እና በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።