1ሺህ 40 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ አገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ስራ 1 ሺህ 40 ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ከተመላሾች ውስጥም 303 ሴቶች ሲሆኑ÷ 90 የሚሆኑት ደግሞ ህጻናት መሆናቸው ተገልጿል፡፡
ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጁላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉን ከከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
እስካሁን ድረስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ስራ ቁጥራቸው ከ 23 ሺህ 640 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉ ተመላክቷል፡፡