አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ምክክር ዛሬ ተካሂዷል፡፡
በምክክሩ ላይ አምባሳደር ግርማ ብሩን ጨምሮ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት፣ ከንግድ ቢሮዎች፣ ከኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት፣ ከኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጅ ባለስልጣን እንዲሁም ከነዳጅ አቅራቢ ድርጅቶች የተውጣጡ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፥ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የተስተዋሉ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ላይ ውይይት ተካሂዷል፡፡