አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ 6 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሁሴን ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷በአረንጓዴ አሻራ መርሃሐ ግብሩ ከሚተከለው ችግኝ 60 በመቶ የሚሆኑት ለኢኮኖሚው አስተዋፅኦ የሚያደርጉ እና ከምግብ ዋስትና ጋር የተያያዙ ችግኞች እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡