የሀገር ውስጥ ዜና

በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 6 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው-የግብርና ሚኒስቴር

By Feven Bishaw

May 16, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ 6 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሁሴን ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷በአረንጓዴ አሻራ መርሃሐ ግብሩ ከሚተከለው ችግኝ 60 በመቶ የሚሆኑት ለኢኮኖሚው አስተዋፅኦ የሚያደርጉ እና ከምግብ ዋስትና ጋር የተያያዙ ችግኞች እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡