Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ341 ሚሊየን በላይ ችግኝ አዘጋጀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ341 ሚሊየን በላይ ችግኝ ማዘጋጀቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል አስታወቀ፡፡
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው÷ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩን በኮንታ ዞን አስጀምረዋል፡፡
አቶ ማስረሻ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት÷ በክልሉ በተጀመረው የክረምት ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ከ341 ሚሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡
ከተዘጋጀው ችግኝ መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዘው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡
በፍሬው አለማየሁ
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.