አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በ24ኛ ሳምነት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አዲስ አበባ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ረፋድ 4 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ሪችሞንድ አዶንጎ ለአዲስ አበባ ከተማ ጎል ሲያስቆጥር ፥ ሄኖክ አየለ ለድሬዳዋ ከተማ ባለቀ ደቂቃ ማስቆጠር ችሏል፡፡
ቡድኖቹ ነጥብ መጋራታቸውን ተከትሎ አዲስ አበባ ከተማ ነጥቡን 24 በማድረስ ባለበት 14ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ፥ ድሬዳዋ በ28 ነጥብ 2 ደረጃዎችን አሻሽሎ 10ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡