የሀገር ውስጥ ዜና

ባለፉት አስር ወራት ከቆዳና ቆዳ ውጤቶች ዘርፍ 33 ነጥብ 14 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኘ

By Feven Bishaw

May 17, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አስር ወራት ከቆዳና ቆዳ ውጤቶች ዘርፍ 33 ነጥብ 14 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገለፀ፡፡

በቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ብርሃኑ እንደተናገሩት፥ ባለፉት አስር ወራት 69 ነጥብ 21 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 33 ነጥብ 14 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል፡፡