የሀገር ውስጥ ዜና

በርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ የተመራ ልዑክ በጋምቤላ ከተማ የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ጎበኘ

By Feven Bishaw

May 17, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ የተመራ ልዑክ በጋምቤላ ከተማ የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኘ፡፡

የክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የተካሄደው አገር አቀፍ የንቅናቄ መድረክ መጠናቀቁን ተከትሎ በክልሉ ርዕሠ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ የተመራ ልኡክ በጋምቤላ ከተማ የሚገኙ አምራች ኢንዱስትዎችን የሥራ እንቅስቃሴ ዙሪያ የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።