ቢዝነስ

ባለፉት 10 ወራት ከተኪ ምርቶች 418 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ተገኘ

By Feven Bishaw

May 18, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀት ዓመቱ ባለፍት 10 ወራት ከተኪ ምርቶች 498 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 418 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር መገኘቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ለተኪ ምርቶች ትኩረት በመስጠት የሀገራችንን ብልጽግና እናፋጥናለን! በሚል መሪ ቃል የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱንና ተጠሪ ተቋማቱን የ2014 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም እየገመገመ ነው፡፡