አዲስ አበባ፣ግንቦት 10፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ክልሉን ከጎበኙ የአገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎች 330 ሚሊየን ብር ገቢ መገኘቱን ገለጸ፡፡
የቢሮው ምክትል ሃላፊና የቱሪዝም ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ፍሬህይወት ዱባለ ÷ የሰላም እጦትና ሌሎችም ችግሮች የቱሪዝሙን ዘርፍ እየፈተኑት ቢመጡም ቢሮው የሀገር ውስጥ ቱሪዝም እንዲስፋፋ በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡