የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ ክልል በልግ አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰብሎች ተሸፍኗል

By Feven Bishaw

May 18, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በልግ አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች 970 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ግብርና ቢሮ የሰብል ልማት ዘርፍ ምክትል ሃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ እንደገለፁት÷የዘንድሮው የበልግ ዝናብ ዘግይቶ ቢጀምርም ቀድሞ የእርሻ ማሳ ዝግጅት በመደረጉና 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል የፋብሪካ ማዳበሪያን ጨምሮ የምርጥ ዘር አቅርቦት አርሶ አደሩ እጅ እንዲደርስ በመደረጉ ውጤታማ መሆን መቻሉን ተናግረዋል።