አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፈረንሳይ በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገሯ የገቡ የኢትዮጵያ ቅርሶችን ልትመልስ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ከ15ኛው ክፍለ ዘመን እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ጅማሮ ባሉት ዓመታት ውስጥ የተሰሩት ቅርሶቹ ከሶስት ዓመታት በፊት በሕገ-ወጥ መንገድ ከኢትዮጵያ ወደ ፈረንሳይ ከተጓጓዙ በኋላ በፓሪስ ሮይሲ አውሮፕላን ማረፊያ የተያዙ ናቸው ተብሏል፡፡