የሀገር ውስጥ ዜና

ከተለያዩ አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትና አጋሮች ጋር በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

By Meseret Awoke

May 19, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ዑማ እና የፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ከተለያዩ አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትና አጋሮች ጋር በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡

ኢንጂነር ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ እንዳሉት፥ “በውይይቱ የማዕድን አቅማችንን በተመለከተ ገለጻ አድርገናል” ብለዋል፡፡

የፋይናንስ ተቋማቱ እየተካሄዱ ያሉ የማዕድን ፕሮጀክቶችን ለማገዝ እንዲሁም የማእድን የግል ክፍለ ኢኮኖሚን በፋይናንስ ለመደገፍ ፍላጎታቸውን መግለጻቸውን ነው ያስታወቁት፡፡