የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮ ቴሌኮም የሞጁላር መረጃ ማዕከልን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ሥምምነት ከ5 ተቋማት ጋር ተፈራራመ

By Feven Bishaw

May 20, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮ ቴሌኮም የሞጁላር መረጃ ማዕከልን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ሥምምነት ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ተፈራረመ።

ተቋሙ ሥምምነቱን የተፈራረመው ከዘመን፣ ዘምዘምና ሂጅራ ባንኮች እንዲሁም ሬስ ማይክሮ ፋይናስና ከዌብስክሪብስ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ነው።